የኢኒሺየቲቭ አፍሪካ ማህበር አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ አካሄደ

ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አንዱ የሆነው ኢኒሺየቲቭ አፍሪካ ማህበር አመታዊ ጠቅላላ ጉኤውን በካሶፒያ ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ አካሄደ፡፡

ማህበሩ እ.ኤ.አ በ2023 ካከናወናቸው ተግባራት መካከል በኢኖቬቲቭ ግራንት ፈንድ በግሉ ዘርፍ የተሰማሩት የንግድ ዘርፍ ማህበራት እና የቢዝነስ ድርጅቶች አባላትን ማብቃት እንዲሁም ንግድ ለሰላምና ልማት እና ንቁ ዜጋ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተጨማሪም 17ኛ አዲስ አለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል ፕሮግራሞች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ማህበሩ በዚሁ ዓመት በዋነኛነት ካጋጠሙት ችግሮች መካከል ለተለያዩ ለጋሾች ያቀረባቸው የድጋፍ ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ አለማግኘቱ ነው ተብሏል፡፡ 

ማህበሩ እ.ኤ.አ በ2024 ካቀዳቸው ስራዎች መካከል ንግድ ለሰላምና ልማት፣ በብሔራዊ ደረጃ የበጎ ፈቃደኞች አገልግሎት እና በጦርነት ምክንያት በትምህርት ወደኋላ የቀሩ ልጃገረዶች የተፋጠነ ትምህርት እንዲያገኙ ማስቻል ፕሮግራሞችና 18ኛው አዲስ አለም አቀፍ ፊልም ፌሰቲቫልን ማካሄድ እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል፡፡

ሌላው በጉባኤው ላይ የቀረበው የማህበሩ እ.ኤ.አ የ2023 የኦዲት ሪፖርት በውጭ ኦዲተር አማካኝነት ሲሆን ማህበሩ በዚህ አመት ከለጋሾች ያገኘውን ድጋፍ 87 በመቶ ለፕሮግራም 13በመቶውን ደግሞ ለአስተዳደራዊ ወጪ መዋሉን በግልጽ ተብራርቷል፡፡ በዚህም አሉ የውጭ ኦዲተሩ ማህበሩ ያለፈው አመት የሥራ ክንውኑ የአለምና የሀገር አቀፍ የፋይናንስና የአስተዳደር ደንብና ስርዓት ጠብቆ ማከናወኑ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የማህበሩ የጠቅላላ ጉባኤ አባላትም የቀረበላቸው የሥራ ክንውንና የኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የዚህ አመት የሥራ እቅድ ላይ ተወያይተው ሁሉንም ሪፖርቶች በሙሉ ድምጽ አጽድቀዋል፡፡

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣንን ለማቋቋም በወጣው አዋጅ መሰረት ኢኒሺየቲቭ አፍሪካ ጊዜውን ጠብቆ አመታዊ ሪፖርቶችን እና እቅዶችን እንዲሁም ደጋፊ መረጃዎችን አሟልቶ ማቅረቡን የባለስልጣኑ መ/ቤት ማረጋገጫ መስጠቱ ታውቋል፡፡    

Initiative Africa Awarded Malala Grant to Empower Female Students in Conflict-Affected Areas

Initiative Africa, a leading non-profit organization dedicated to empowering vulnerable youth, has recently received a substantial boost in its efforts to support young women affected by conflict. The organization has been awarded a prestigious Malala grant totaling $300,000 as part of its enrollment in the Education Champion Network. This grant is set to significantly enhance Initiative Africa’s project aimed at helping female students who have been impacted by conflict to regain access to education and develop essential skills for future success.

The project, spearheaded by Initiative Africa, focuses on implementing a comprehensive Accelerated Learning Program (ALP) coupled with a Life Skills program. This innovative approach is designed to address the unique challenges faced by female students who have been displaced or otherwise affected by conflict. By providing access to education and essential life skills training, Initiative Africa aims to empower these individuals to rebuild their lives and pursue opportunities for personal and professional growth.

The significance of this grant cannot be overstated, as it represents a vital step forward in Initiative Africa’s mission to make a meaningful impact on the lives of vulnerable youth. With the support of the Malala grant, the organization will be able to expand its reach and provide critical resources to a greater number of young female students in need.

Crucially, the success of Initiative Africa’s project in gaining the fund has been further facilitated by the invaluable assistance of the Swedish International Development Cooperation Agency (sida). Through its constant support for the Business for Peace project, sida has played a pivotal role in helping Initiative Africa sharpen its expertise in the field of conflict resolution and peacebuilding. By leveraging sida’s support, Initiative Africa has been able to strengthen its programs and maximize its impact on the ground.