በአስገድዶ መድፈር ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በ 25 አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በ 25 አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ

በአሰገድዶ መድፈር ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት የ25 አመት ፅኑ እስራት ተፈረደበት፡፡

ተከሳሽ ደስታ ገበየሁ የተባለ ግለሰብ ቀኑ ነሀሴ ወር 2011 ዓ.ም ዕድሜቸው ስምንት እና ዘጠኝ አመት የሆነ ሁለት ሴት ህፃናቶችን በተለያዩ ቀናቶች በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ክልል ውስጥ በሚገኝው ተከራይቶ ከሚኖርበት ቤት ውስጥ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመባቸው በመሆኑ የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዐቃቂ ቃሊቲ ምድብ ፅ/ቤት የኢፌዲሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 627(1) ተላልፎ በመገኘቱ አራት ክሶችን መስርቶበታል፡፡

ተከሳሹ ፍርድ ቤት ቀርቦ ክሱን ክዶ የተከራከረ ቢሆንም ዐቃቤ ህግ በተከሳሽ ላይ ማስረጃ አቅርቦ በማሰማቱ እንዲሁም ተከሳሽ የተከሰሰበትን ክስ ሊያስተባብል ባለመቻሉ ፍርድ ቤቱ ተከሳሽን በአራቱም ክሶች ጥፋተኛ ነህ በማለት ሰኔ 16 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ60 አመት እንዲቀጣ የፈረደበት ቢሆንም የተከሰሰበት ድንጋጌ ጣሪያው 25 ዓመት በመሆኑ በ 25 አመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

በሌላ በኩል በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ከሴቶችና ህፃናት ወንጀል ጋር ተያይዞ ከመጋቢት ወር 2012 ዓ.ም ጀምሮ 19 የምርመራ መዝገቦች ቀርበው የተጣሩ ሲሆን በ8 መዝገቦች ላይ ክስ ተመስርቶ ለችሎት መቅረባቸውን የአቃቂ ቃሊቲ ምድብ ጽፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ሲሳይ ጎኣ የገለጹ ሲሆን ቀሪዎቹ መዝገቦች በምርመራና በመወሰን ሂደት ላይ እንደሆኑ ምክትል ኃላፊ አብራርተዋል፡፡

በመሆኑም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግና ድርጊቱ ተፈፅሞ ሲያገኝም በተቻለ ፍጥነት ለፓሊስ ማሳወቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
(ጠቅላይ አቃቤ ህግ )
ሰኔ 19 ቀን 2012 ዓ.ም

source አቤል ብርሀኑ (የወይኗ ልጅ)

በተሻሻለው መመሪያ መሰረት በቤት ውስጥ ሆነን የኮሮና ቫይረስ ሕክምና ለመከታተል የሚያስችሉ መስፈርቶች

በቤት ውስጥ የኮቪድ-19 በሽታ ህክምና አገልግሎት ለማግኘት የሚያስችሉ መስፈርቶች የሚከተሉት ናቸው፦

1. በቤት ሆኖ የኮቪድ-19 ህክምና ለማግኘት ፍቃደኛ የሆነ፣

2. ቀላል ወይም ምንም አይነት የኮቪድ-19 ምልክት የሌለበት፣

3. በቤት ውስጥ የቆይታ ጊዜ አጋዥ ወይም ረዳት ያለው እንዲሁም እራሱን መርዳት የሚችል፣

4. የምግብ እና ሌሎች መሰረታዊ ፍላጎቶችን ማግኘት ወይም ማሟላት የሚችል፣

5. በተመሳሳይ ቤት ውስጥ የሚኖር ሌላ ሰው የግል ንፅህና መጠበቂያዎችን እንዲሁም የአፍና የአፍንጫ ማሸፈኛ ጭንብሎችን ማግኘት የሚችል እንደሆነ፣

6. ኮቪድ-19 የተገኘበት ሰው ከሌሎች ተዷጋኝ በሽታዎች ማለትም የልብና የደም ቧንቧ በሽታ ፣ የስኳር በሽታ፣ አስም፣ ኤች አይቪ፣ ቲቢ፣ ካንሰርና የመሳሰሉት በሽታዎች ካሉባቸው ሰዎች ጋር አብሮ የማይኖር ከሆነ፣

7. የኮቪድ-19 የተገኘበት ሰው ከቤት ላለመውጣት ወይም ማናቸውም ጠያቂ ወደቤት እንዳይመጣ ለማድረግ ማረጋገጫ የሚሰጥ ከሆነ፣

8. እራሱን ከሌሎች የቤተሰብ አባላት ለይቶ ማቆየት የሚያስችል ክፍል ወይም ከቤተሰብ አባላት በ2 ሜትር ርቀት ላይ መቆየት የሚያስችል ክፍል ያለው እንደሆነ፣

9. በጤና ቡድን በቋሚነት ለመደገፍ ፈቃደኛ የሆነ፣

Source TIKVAH-ETH

Women Supporting Women

 A woman has power; collectively we have impact. Traditionally we have been taught to be competitive with one another, because there was a scarcity of opportunity,  the truth is, we can create opportunity and rise higher together as women.

image source – https://dribbble.com/

Question 1

Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipiscing elit, sed do eiusmod tempor incididunt ut labore et dolore magna aliqua. Ut enim ad minim veniam, quis nostrud exercitation ullamco laboris nisi ut aliquip ex ea commodo consequat. Duis aute irure dolor in reprehenderit in voluptate velit esse cillum dolore eu fugiat nulla pariatur. Excepteur sint occaecat cupidatat non proident, sunt in culpa qui officia deserunt mollit anim id est laborum.

The effects of COVID-19 on gender-based violence (GBV)

For Ethiopia to report gender-based violence

991- Police

+251-115-52 83 94/+251-118-59 01 84 Ministry of

Women Children and Youth

907- Red cross Ambulance service

 

በ2 ወር ውስጥ 101 ሕጻናት ተደፍረዋል!

በ2 ወር ውስጥ 101 ሕጻናት ተደፍረዋል!

ኮሮና ወደ ሀገራችን ከገባ በኅላ ሌላ ገጽታ እያሳየን ይገኛል። ብዙዎች በቤታቸው እንዲቀመጡ በሚመከርበት ወቅት በቤት ውስጥ በሕጻናትና ሴቶች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ልብ ሊባል እንደሚገባ ከምንሰማቸው አንዳንድ መረጃዎች መገንዘብ ይቻላል።

በትላንትናው ዕለት በዋልታ ቴሌቪዥን ’51 በመቶ’ በሚል በተዘጋጀ ዝግጅት ላይ የአዲስ አበባ ሴቶችና ሕጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ አልማዝ አብርሃ እንደገለጹት ከ3 ሆስፒታሎች በተገኘ ሪፓርት ብቻ በሁለት ወር 101 ሕጻናት መደፈራቸውን ገልጸዋል።

ይህ ቁጥር ትምህርት ቤቶች በተዘጉበት ፣ ሕጻናት ከቤት በማይወጡበትና ጥቆማዎች ሊደርሱ በማይችሉበት ሁኔታ ይሄን ያህል መጠን መጠቀሱ በራሱ አስደንጋጭ ነው ብለዋል። ከሕጻናት በተጨማሪም በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች እየተበራከቱ መምጣታቸውን ገልጸዋል።

ወይዘሮ አልማዝ ጨምረው እንደገለጹት ከተደፈሩት ሴት ህፃናት በተጨማሪ 57 የሚደርሱ አብዛኞቹ እድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ‘ወንድ ልጆች’ እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

 

“የ14 እና የ17 ዓመት ልጆች በአባቶቻቸው ተደፍረዋል” – ወይዘሮ ማኅሌት ኃይለማርያም

የኢትዮጵያ ሴቶች መጠለያ ጥምረት ም/ሰብሳቢ ወይዘሮ ማኅሌት ኃይለማርያም ‘ከዋልታ ቴሌቪዥን’ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ጥቃት የተፈጸመባቸው ሴቶችና ሕጻናትን የሚቀበሉ መደበኛ መጠለያዎች በኮሮና ምክንያት አዳዲስ ኬዞችን መቀበል በማቆማቸው በርካታ ዜጎች ተቸግረው እንደነበር ገልጸዋል።

አሁን ላይ አዲስ ኬዞችን የሚቀበል ለስድስት ወር የሚቆይ መጠለያ በቅርቡ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በመጠለያውም እስከ አሁን 27 የሚደርሱ በጾታዊ ጥቃት ፣ በአስገድዶ መድፈር፣ ልጅ በመካድና በባላቸው ጥቃት የተፈጸመባቸውን ሚስቶች ተቀብሎ እያስተናገደ ነው ብለዋል።

በማዕከሉ ከገቡ ሕጻናት ውስጥ በአባቶቻቸው የተደፈሩ የ14 እና የ17 ዓመት ልጆችን እንደምሳሌነት የጠቀሱት ሰብሳቢዋ ላላስፈላጊ ውርጃ ተጋልጠው ሽንታቸውን መቆጣጠር የማይችሉበት ደረጃ ደርሰው ነበር ብለዋል።

በተለይ የ17 ዓመቷ ልጅ አባትየው የአደንዛዥ እፅ ጭምር እንድትጠቀም ማድረጉን ገልጸዋል። ጥቃቶች አይነትና መልካቸውን እየቀየሩ መምጣታቸውንም ነው የተናገሩት።

Source TIKVAH-ETH (Tsegab Wolde)

 

COVID-19 and Ending Violence against Women and Girls in Ethiopia

POLICY BRIEF_EVAWG COVID 26-05-2020 100% black

For more information

https://www.unwomen.org/en/digital-library/publications/2020/04/series-evaw-covid-19-briefs

Fiscal Year 2020 Innovative Grant Announcements and Awards

Initiative Africa announces grant funding opportunities through the Innovative Grant Fund (IGF) funded by the Swedish Embassy, under the project titled “Empowering Marginal Economic Actors Through Policy Reform from the Bottom Up – EMEA”. This grant is to assist Chambers of Commerce and Business Membership Organizations (BMOs) in developing strong programs that contribute to business and economic development,

Visit the IGF Grant Section of our website for all the information you need to apply for a grant.

Contact us:

Phone no.: – 011-662-2640/41

Email: – Aberash.j@initiativeafrica.net   or  Abenezer.t@initiativeafrica.net