We will be having a consultative workshop with school leaders in Addis Ababa on “Gender Equality: Making Change Happen” project. The project focuses on gender empowerment programs which address social norms and behavior change, seek out and build partnerships among organizations that work on gender issues, and develop programs that involve men and boys in the promotion of gender equality.

ጩህ ጩህ አለኝ

                                                                            አያሌው አስረስ 

                                                                             (ለኢኒሺየተቭ አፍሪካ የቀረበ)

          መስቀል አደባባይ አጠገብ በሚገኘው አዲስ አበባ ሙዝየም ውስጥ ሰሞኑን አንድ አውደ ትርኢት ቀርቦ ነበር፡፡ አውደ ትርኢቱን ያዘጋጁት ሴታዊት የሚባል መንግሥተዊ ያልሆነ ድርጅት, ከዩኔ ውመን እና የስዊዲን ኤምባሲ (Sweden Embassy) በጋራ በመሆን ነው፡፡ ‹‹ ምን ለብሳ ነበር? ›› በሚል ርእስ የቀረበው ይህ አውደ ርእይ ያተኮረው አለባበስን ተንተርሶ  በሴቶች ልጆች ላይ የተፈጸመውን የወሲብ ጥቃት በማሳየት ላይ ነው፡፡እኛ ደግሞ  ጾታ እንጂ አለባበስ የመደፈር ምክንያት አይደለም፤ ያ ቢሆን  ኑሮማ  የአለቀ የተማሪ የደምብ ልብስ (ዩኒፎርም )  የለበሰቸው  መክሊት በምን ምክንያት ትደፈራለች? ብለን እንሞግታለን:: ፊት ለፊት አያምጡት እንጂ የእነሱም መሻት ይህን መስረገጥ ነው፡፡

ጥቃቱ የተፈጸመባቸውን ልጆች በእድሜ  ስናይ  ደግሞ የሰባት አመቷን አሚናን  እና የአስራ ዘጠኝ አመቷን መንበረን እናገኛልን፡፡ጥቃቱ የደረሰባቸው 16 ሴቶች ሲሆኑ ጥቃት አድራሽ ወንዶች ደግሞ 17 ናቸው፡፡ ይህ ማለት አንደኛዋ በሁለት ወንዶች ተደፍራለች ማለት ነው፡፡ ጥቀቱን ከፈጸሙት 17 ወንዶች ለሕግ የቀረቡት ሁለት ብቻ ናቸው፡፡ በሕግ ቁጥጥር ሥር ገብቶ የነበርው ሶስተኛው አጥቂ ለፖሊስ ጉቦ ሰጥቶ መውጣቱና መልሶም አለመያዙ ተገልጧል፡፡ አራተኛው ደግሞ በዋስ ወጥቶ በዚያው ጠፍቷል፡፡

የመደፈር አደጋ ከደረሰባቸው ውስጥ አንዷ  ኮከብ የተደፈረቸው ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ነው፤እስረኛ ሆና ተገኝታ  አይደለም ሕግ የጠብቀኛል ብላ ገብታ እንጂ፡፡  ከታሪኩ የድርጊቱን አፈጻጻም መገመት ይቻላል፡፡ ኮከብ  ከመኖሪያዋ ብዙም ወደ ማታውቀው አካባቢ ርቃ   ሔዳለች፡፡ ልትመለስ ስታሰብ ጊዜው መሽቷል፡፡ በዚያ የምታውቀው ያሳድረኛል የምትለው  ሰው ወይም ዘመድ የላትም፡፡ ስለዚህም ፖሊስ ጣቢያ ተጠግታ አድራ በሰላም ወደ አካበቢዋ ለመመለስ ወስና ጣቢያ ትሔዳለች፡፡ በቦታው የነበሩት ፖሊሶች በሃሰቧ ተስማምተው ከሴት እስረኞች ጋር እንድታድርና ጠዋት ወደ አገሯ እንድትሔድ  ይወሰናሉ፡፡ ተረኛ ፖሊሱ ግን ወስዶ ከሴት  እስረኞች ጋር እንድታድር አላደረገም፡፡ ከእረሱ ጋር እንድታድር አድርጎ ደፈራት፡፡ ጠዋት ላይ ወስዶ ከሴት እስረኞች ጋር ሲቀላቅላት እስረኞች ተቀወሙ፡፡ ስለዚህም ወንጀሉ ተጋለጠ፡፡ ምን ያደርጋል እሱም ለሕግ አልቀረበም፡፡ጩህ ጩህ የአለኝ ለዚህ  ነው፡፡

በአክሰትና ባጎት እጅ አድገው ለቁም ነገር የደረሱ ብዙዎች ቢኖሩም የቤዛዊት እጣ ግን ያማል፡፡ ‹‹ መጣችልህ የፈለግከውን አድረጋት›› ብላ አሳለፋ ለደፋሪው የሰጠቻት ወገኔ ብላ የተጠጋቻት  እንደ አንድ የቤት ሠራተኛ አገልጋይዋ አድርጋ ጉለበቷን ሰትበዘብዛት የነበረችው  አክስቷ ናት፡፡   የሰባት አመቷ የአሚና እና የአስራ ስምነት አመቷ የአርሴማ ጥቃት ደግሞ ለመናገር እራሱ ይከብዳል፡፡ ሰው ከሰውነት ወርዶ ፍጹም እንስሳ ሆኖ በእንስሳነት በሕሪውና ተግባሩ የተገለጠበት ድርጊት ነው፡፡ አርሞ ኮትኩቶ ለቁም ነገር ማድረስ የነበረበትን አባት  የገዛ ልጁን ሲደፍር  በምን ቃል ምሬትንና ጥላቻን  መግለጥ ይቻላል ? የክርሰትናና የእስልምና ወይም የሌላ እምነት ተከታይ ሃይማኖተኛ ሕዝቦች ነን  የምንል ሰዎች  የሞራል ልዕልናችን ወደ የት አለ?  ብሎ መጠየቅ ግድ ይሆናል፡፡ይህ አይነቱ ቅሌትና የሞራል ዝቅጠት አያሰጮህም?

በመጠቃተቸው የደረሰባቸው ጉዳት ሳያንሰ አንዳንዶቹ ለማርገዝና ለመውለድ ተገድደዋል፡፡አክስቷ ለመደፈር የዳረገቻት ቤዛዊት ልጇን ለማየት ምን ያህል ትጠላ እንደነበር የምተናገረው ምርር ባለ ቃል ነው፡፡ መከራውንና የመከራውን ማስተወሻ በአንድነት ለመያዝ መገደድ እሷን አታድርገኝ ያሰኛል፡፡

ጥፋቱ እንደተራ ጉደይ ታይቶ ፋይሉ የትም ተጥሎ ይሆናል፡፡ ተበዳዮች ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተመላልሰው ነገሩን ለመቀስቀስ ሲነሱ ምን እንደሚጠብቀቸው ኤተወቅም፡፡ ምን አልባት  መጠቋቆሚያም እየተደረጉ እየተሸማቀቁ ተጨማሪ ጉዳት ላለማስተናገድ ቢቀርስ ብለው ነገሩን ትተውት ሸሽተው  ቤታቸው ገብተው ዘግተውም  ይሆናል፡፡መጮህ አሁንም መጮህ የሚያስፈልገው በሕገ አስፈጻሚው ላይ ነው ፡፡ ‘እነእከሌ ምን ሆኑ’ የሚሉ ተጨማሪ ጥቃት ፈጻሚዎች እያበዛብን እንዳይሆን ያሰጋል። ሁሉም ወገን በህፃናትና ሴቶች ላይ የሚደርስ ጥቃት ለመከላከል ዘብ ሊቆም ይገባል። በተለይ በት/ቤቶችና በማህበረሰቡ ውስጥ የባህርይ ለውጥ ማምጣት የሚያስችሉ እንቅስቃሴዎች ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከል ከተቋቋሙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር መተባበር ያስፈልጋል።

Gender Network in Hawassa City

Initiative Africa’s  Making Change Happen project is working towards a more holistic approach to prevent prevent and combat violence against women, ensure freedom of choice, and foster gender gender equality within all sectors of society.  One of the main activities under this project is the expansion of SIDA’s existing gender network into the regions outside of Addis Ababa to increase its outreach capabilities. In collaboration with its regional partner, Center of Concerns in Hawassa, Initiative Africa established a gender network consisting of influential men and women who play a vital role in their community. The network was established, with COC’s support,  on December 12, 2018 in Hawassa with 12 select individuals in attendance.

Objective of the network

  • Assist project implementation by bringing together network leaders across multiple industries and sectors of society

  • Create a networking platform for women, community leaders and entrepreneurs to share best practice around running their networks, challenges and opportunities as well as leverage peer-to-peer support to enable network success and growth.

 

The overall goal will be to strengthen the outreach capabilities of the network and create a platform for experience sharing and peer-to-peer connections to aid the women in the community in advancing their professional and personal goals and remove barriers to women’s participation in community development.

Active Citizens – Get the Youth Skilled and Working Locally – Gurage Zone

      

Initiative Africa and British Council’s project called “ACTIVE CITIZENS: Get the Youth Skilled and Working Locally”, #YCDF conducted ‘Social Enterprise Leadership Training’, from December 07-09 and 15-16, 2018. The sensitization workshop and learning sessions attended by 72 participants (32 school children and 42 school community members) in Gurage Zone, Emdebir Secondary and Preparatory School.
With a view of creating future social enterprise schools, the social enterprise program will work directly with this young people [school children] by building their capacity through social enterprise leadership skills,  to increase their social engagement and to initiate school based community action project.